Telegram Group & Telegram Channel
ጥበቃ.......

"እንዴት የሚያምር ቀን ነው"። በሚል ሀይለቃል ነበር ቀኔን የጀመርኩት። በጣም ደስ ብሎኝ ነበር በጠዋት የነቃሁት። ምክኒያቱም ለ 5 አመታት ሳልሰለች የጠበቅኩት ፍቅረኛዬ ይመጣል ። ለ አመታት ያሳለፍኳቸውን የጥበቃ ጊዚያቆች ሳስብ አንዳንዴ በፅናቴ እገረማለሁ። ከአሁን አሁን ይደውላል ጥበቃ፣ ከዛሬ ነገ ታገቢኛለሽ ብሎ ይጠይቀኛል ጥበቃ፣ ድንገት መጥቶ ሰርፕራይዝ ያደርገኛል ጥበቃ፣ ተኝቼ በህልሜ እስካየው ጥበቃ፣.................ብቻ ብዙ ብዙ ጥበቃ ለወትሮው እንደዚህ ትዕግስተኛ አልነበርኩም የያዘ ይዞኝ እንጅ........




ዛሬ ግን ይሄ ጥበቃየ ለመጨረሻ ጊዜ የሚያበቃበት ቀን ነው። በቃ እፎይ የምልበት ቀን። ለዛም ነው በጠዋት ተነስቼ ቆንጆ ሆኜ የመጨረሻ ጥበቃየን ለመጠበቅ እየተዘጋጀሁ ያለሁት ። የሚወደውን ቆንጆ ሀምራዊ ቀሚስ አድርጌ፣ ፀጉሬን በግራ በኩል ከፍዬ ቆንጆ አድርጌ አስይዤዋለሁ። ጫማዬ ጥቁር ትንሽ ተለቅ ያለ ሄል ያለው ቆንጆ ጫማ ነው። ቦርሳዬ ዋው እሱ ድሮ የላከልኝ በጣም ምወደው ጥቁር ነጫጭ ፈርጥ ያለው ነው። በጊዜው ውድ የሚባለውን ሽቶ በላዬ ላይ አርከፍክፌ መስታወት ፊት ቆምኩ። መልኬ እንደዛሬ ቆንጆ ሆኖ ታይቶኝ አያውቅም። ብቻ ወጣሁ..............



ቦታው ጋ ደርሼ ሲመጣ ምን እንደምለው ፣ ከዛ በኋላ የምናደርጋቸውን ነገሮች፣ የሚኖረንን ሕይወት እያሰብኩ በደስታ አለም ውስጥ ራሴን አሰመጥኩት። ጠበቅኩ.....ጠበቅኩ...... ጥበቃው ሊሰለቸኝ ሲጀምር..... ለ አምስት አመት የጠበቅኩ ሴት አንድ ቀን መታገስማ አያቅተኝም ከዚህ በኋላኮ ላርፍ ነው ተመስገን እያልኩ ብቻየን እስቃለሁ። ብዙ ሰዓታት አለፉ ስልኩ አይሰራም........ሲመጣ መንገድ ላይ የሆነ ነገር ገጥሞት እንደሆነ ደመደምኩ። ነፍሴ ተጨነቀች...... ሳላገኘው ምን ሆኖብኝ ይሆን? ብቻ ውስጤ ፈራ....... ግን መጠበቅ አላቆምኩም ።ካለፉት አምስት አመታት ጥበቃ ይልቅ የዛሬው ጥበቃ እንደ ሺ አመት ረዘመብኝ። ............
ጥበቃው ቀጠለ። አንድ መልዕክት ስልኬ ጋር እስኪገባ ድረስ። እንዲህ ይል ነበር......


" የኔ ማር አትጠብቂኝ ለዘላለም አልመጣም!!!!"

የዛ ሁሉ አመት ጥበቃ በአንድ አረፍተነገር አከተመ!!!! "አልመጣም" መልዕክቱን ደጋግሜ አየሁት ውስጤ ላይ የሆነ ነገር ቁርጥ ሲል ብቻ ተሰማኝ። አልጮህኩም፤ አላለቀስኩም። ምን እንደተሰማኝም አላውቅም ብቻ ግን ተሰበርኩ። ክንፏ እንደተመታ ወፍ ሙሽሽ አልኩ። ለካስ በጣም ሲታዘን እንባም ይደርቃል፣ ለመጮህም ቃላት ያልቃል።


ግን አንድ ነገር ልክ ነበርኩ። እንዳልኩት ዛሬ የመጨረሻ የጥበቃ ቀኔ ሆነ።ከዛሬ በኋላ አልጠብቅም!!!!




ከተቀመጥኩበት ተነስቼ በተሰበረ ልቤ ወደቤቴ መንገዴን ቀጠልኩ።

@nibab_lehiwot
@nibab_lehiwot
@nibab_lehiwot



tg-me.com/nibab_lehiwot/158
Create:
Last Update:

ጥበቃ.......

"እንዴት የሚያምር ቀን ነው"። በሚል ሀይለቃል ነበር ቀኔን የጀመርኩት። በጣም ደስ ብሎኝ ነበር በጠዋት የነቃሁት። ምክኒያቱም ለ 5 አመታት ሳልሰለች የጠበቅኩት ፍቅረኛዬ ይመጣል ። ለ አመታት ያሳለፍኳቸውን የጥበቃ ጊዚያቆች ሳስብ አንዳንዴ በፅናቴ እገረማለሁ። ከአሁን አሁን ይደውላል ጥበቃ፣ ከዛሬ ነገ ታገቢኛለሽ ብሎ ይጠይቀኛል ጥበቃ፣ ድንገት መጥቶ ሰርፕራይዝ ያደርገኛል ጥበቃ፣ ተኝቼ በህልሜ እስካየው ጥበቃ፣.................ብቻ ብዙ ብዙ ጥበቃ ለወትሮው እንደዚህ ትዕግስተኛ አልነበርኩም የያዘ ይዞኝ እንጅ........




ዛሬ ግን ይሄ ጥበቃየ ለመጨረሻ ጊዜ የሚያበቃበት ቀን ነው። በቃ እፎይ የምልበት ቀን። ለዛም ነው በጠዋት ተነስቼ ቆንጆ ሆኜ የመጨረሻ ጥበቃየን ለመጠበቅ እየተዘጋጀሁ ያለሁት ። የሚወደውን ቆንጆ ሀምራዊ ቀሚስ አድርጌ፣ ፀጉሬን በግራ በኩል ከፍዬ ቆንጆ አድርጌ አስይዤዋለሁ። ጫማዬ ጥቁር ትንሽ ተለቅ ያለ ሄል ያለው ቆንጆ ጫማ ነው። ቦርሳዬ ዋው እሱ ድሮ የላከልኝ በጣም ምወደው ጥቁር ነጫጭ ፈርጥ ያለው ነው። በጊዜው ውድ የሚባለውን ሽቶ በላዬ ላይ አርከፍክፌ መስታወት ፊት ቆምኩ። መልኬ እንደዛሬ ቆንጆ ሆኖ ታይቶኝ አያውቅም። ብቻ ወጣሁ..............



ቦታው ጋ ደርሼ ሲመጣ ምን እንደምለው ፣ ከዛ በኋላ የምናደርጋቸውን ነገሮች፣ የሚኖረንን ሕይወት እያሰብኩ በደስታ አለም ውስጥ ራሴን አሰመጥኩት። ጠበቅኩ.....ጠበቅኩ...... ጥበቃው ሊሰለቸኝ ሲጀምር..... ለ አምስት አመት የጠበቅኩ ሴት አንድ ቀን መታገስማ አያቅተኝም ከዚህ በኋላኮ ላርፍ ነው ተመስገን እያልኩ ብቻየን እስቃለሁ። ብዙ ሰዓታት አለፉ ስልኩ አይሰራም........ሲመጣ መንገድ ላይ የሆነ ነገር ገጥሞት እንደሆነ ደመደምኩ። ነፍሴ ተጨነቀች...... ሳላገኘው ምን ሆኖብኝ ይሆን? ብቻ ውስጤ ፈራ....... ግን መጠበቅ አላቆምኩም ።ካለፉት አምስት አመታት ጥበቃ ይልቅ የዛሬው ጥበቃ እንደ ሺ አመት ረዘመብኝ። ............
ጥበቃው ቀጠለ። አንድ መልዕክት ስልኬ ጋር እስኪገባ ድረስ። እንዲህ ይል ነበር......


" የኔ ማር አትጠብቂኝ ለዘላለም አልመጣም!!!!"

የዛ ሁሉ አመት ጥበቃ በአንድ አረፍተነገር አከተመ!!!! "አልመጣም" መልዕክቱን ደጋግሜ አየሁት ውስጤ ላይ የሆነ ነገር ቁርጥ ሲል ብቻ ተሰማኝ። አልጮህኩም፤ አላለቀስኩም። ምን እንደተሰማኝም አላውቅም ብቻ ግን ተሰበርኩ። ክንፏ እንደተመታ ወፍ ሙሽሽ አልኩ። ለካስ በጣም ሲታዘን እንባም ይደርቃል፣ ለመጮህም ቃላት ያልቃል።


ግን አንድ ነገር ልክ ነበርኩ። እንዳልኩት ዛሬ የመጨረሻ የጥበቃ ቀኔ ሆነ።ከዛሬ በኋላ አልጠብቅም!!!!




ከተቀመጥኩበት ተነስቼ በተሰበረ ልቤ ወደቤቴ መንገዴን ቀጠልኩ።

@nibab_lehiwot
@nibab_lehiwot
@nibab_lehiwot

BY ሕይወትን - በገፅ


Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 283

Share with your friend now:
tg-me.com/nibab_lehiwot/158

View MORE
Open in Telegram


ሕይወትን በገፅ Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Start with a fresh view of investing strategy. The combination of risks and fads this quarter looks to be topping. That means the future is ready to move in.Likely, there will not be a wholesale shift. Company actions will aim to benefit from economic growth, inflationary pressures and a return of market-determined interest rates. In turn, all of that should drive the stock market and investment returns higher.

Telegram hopes to raise $1bn with a convertible bond private placement

The super secure UAE-based Telegram messenger service, developed by Russian-born software icon Pavel Durov, is looking to raise $1bn through a bond placement to a limited number of investors from Russia, Europe, Asia and the Middle East, the Kommersant daily reported citing unnamed sources on February 18, 2021.The issue reportedly comprises exchange bonds that could be converted into equity in the messaging service that is currently 100% owned by Durov and his brother Nikolai.Kommersant reports that the price of the conversion would be at a 10% discount to a potential IPO should it happen within five years.The minimum bond placement is said to be set at $50mn, but could be lowered to $10mn. Five-year bonds could carry an annual coupon of 7-8%.

ሕይወትን በገፅ from tw


Telegram ሕይወትን - በገፅ
FROM USA